አሚር አል-ሙእሚኒን Amir Al-Mu'minin

አሚር አል-ሙእሚኒን Amir Al-Mu'minin ​"አንተ ዳውድ ሆይ! እኛ በምድር ላይ ምትክ (ገዥ) አደረግንህ፤ ስለዚህ በሰዎች መካከል በውነት ፍረድ፤ ስሜትንም አትከተል..." — (ሱረቱ ሳድ፣ 38:26)

ሰበር ድንቅ መረጃ ደርሶናል ከአንድ ግብረ አበሩ ጋር የተደረገው ሙሉ የስልክ ልውውጥ ከነ ሙሉ መረጃው አቤት ድፍረት አቤት ንቀት ወገን እረ ሙተናል ጠብቁኝ አጋራችሆለሁ እንደው የገቢወቹ ሹም...
21/01/2026

ሰበር ድንቅ መረጃ ደርሶናል ከአንድ ግብረ አበሩ ጋር የተደረገው ሙሉ የስልክ ልውውጥ ከነ ሙሉ መረጃው
አቤት ድፍረት አቤት ንቀት ወገን እረ ሙተናል ጠብቁኝ አጋራችሆለሁ እንደው የገቢወቹ ሹም ግን በህይወት አለህ አንተ አመራር ነህ ግን አቤት ውርደት አቤት ዝቅጠት አቤት ንቅዘት ሆዳም ሌባ ሁሉ።

ላብ እና ካብ  የሁለቱ ህንጻዎች ወግ​በአንዲት የንግድ ከተማ ተብላ የምትጠራ ደሴ ከተማ  ውስጥ ሁለት ጎረቤታም ህንጻዎች ይገኛሉ። አንደኛው ህንጻ ባለቤት ለዘመናት በብረትና ብረታ ብረት ንግ...
20/01/2026

ላብ እና ካብ የሁለቱ ህንጻዎች ወግ
​በአንዲት የንግድ ከተማ ተብላ የምትጠራ ደሴ ከተማ ውስጥ ሁለት ጎረቤታም ህንጻዎች ይገኛሉ። አንደኛው ህንጻ ባለቤት ለዘመናት በብረትና ብረታ ብረት ንግድ ውስጥ የከረሙ፣ በላባቸውና በወዛቸው ሃብት ለማፍራት የሚጥሩ ታታሪ ነጋዴ ናቸው። ሁለተኛው ህንጻ ደግሞ "ልዑል ሰገድ" የተባለ የገቢዎች መስሪያ ቤት ተቀጣሪ ወጣት ንብረት ነው።
​የአንድ ዓመቱ ተአምር እና የሰባቱ ዓመት ድካም
​ነጋዴው መሬት ገዝተው፣ ህንጻ ለመገንባት ድንጋይ ካነጠፉ ሰባት ዓመታትን አስቆጥረዋል። ባንክ ደጅ ጥንተው፣ ከቀረጥ ጋር ግብግብ ገጥመውና የገበያ መውጣት መውረድን ተቋቁመው ዛሬም ህንጻቸው ገና ፍንጭት ጥርሱን እንዳሳየ ህጻን ልጅ "ምድር-ቤቱ" ላይ ቆሟል።
​ልዑል ሰገድ ግን የመንግስት ሰራተኛ ነው። ወርሃዊ ደመወዙም ቢሆን ከአስር ሺህ ብር ጥቂት ከፍ የሚል ነው። ነገር ግን ልዑል ሰገድ መሬቱን በገዛ በሳምንቱ የነበረውን ቤት አፈረሰ። በሶስተኛው ወር ህንጻው ግማሽ ደረሰ። ስድስተኛው ወር ላይ ቪላው አምሮና ደምቆ ተጠናቀቀ። ነጋዴው "ለፊኒሺንግማ ይቆማል" ብለው ሲጠብቁ፣ በአንድ ወር ውስጥ ቀለሙ ተቀብቶ፣ መስታወቱ ገብቶ ለምርቃት በቃ።
​የአባትና ልጅ ምልልስ ነጋዴው በሁኔታው ግራ ተጋቡ። "እንዴት የልዑል ሰገድን እድሜ ያክል ነግጄ፣ ፀሐይና ቁሩን ተቋቁሜ መጨረስ ያቃተኝን ቤት፣ እሱ በስድስት ወር ጨረሰው?" ብለው ራሳቸውን ጠየቁ። በመጨረሻም ልጃቸውን በስልክ ጠርተው እንዲህ አሉት ​"ልጄ ሆይ! ከአሁን በኋላ ንግዱን እርሳው። ይልቅ ሂድና አካውንቲንግ ተማር! እኔ 40 ዓመት ሙሉ የነገድኩት፣ 7 ዓመት ሙሉ የተንገላታሁት በባዶ ተስፋ ኖሯል። መኖር ካለብህ እንደ ልዑል ሰገድ 'ገቢዎች' ውስጥ ተቀጠር።"
​ልጁም በአባቱ ግርምት እየሳቀ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፦​"አይ አባቴ! ልዑል እኮ ምንም ፍቃድ ሳያወጣ፣ ታክስ ሳይከፍልና ደረሰኝ ሳይቆርጥ በበወር ቢያንስ 100 ሺህ ብር 'የተጣራ ትርፍ' ይሰበስባል። የእሱ ህንጻ በሲሚንቶ ሳይሆን በደሃ እምባና በሹክሹክታ ነው የተገነባው።"
​"ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ"
​ነጋዴው ላሟን እየሳቡ፣ እየቀለቡና እያረሱ ኩበት ያጣሉ። ልዑል ሰገድ ግን ላሟ ባልዋለችበት ሜዳ ላይ የኩበት ክምር ያመርታል። የነጋዴው ህንጻ በላብ ስለታጠበ ለመድረቅ ጊዜ ይፈጅበታል፤ የልዑል ሰገድ ህንጻ ግን በ"ቅባት" (ሙስና) ስለታጠበ እንደ ፌርማታው ቶሎ ያልቃል።
​ዛሬ የነጋዴው ህንጻ አሁንም ምድር ቤቱ ላይ ሆኖ ሰማይን አሻቅቦ ያያል። የልዑል ሰገድ ህንጻ ግን በኩራት ተገንብቶ ጎረቤቱን ዝቅ አድርጎ ይመለከታል። ሆኖም ግን የታሪክ መዝገብ እንዲህ ይላል፡- "በአመጻ የተገኘ ሃብት እንደ በረዶ ይቀልጣል፤ በድካም የተከማቸ ግን ይበረክታል።"​ ​የልዑል ሰገድ ተቃራኒ የህሊናው ንጉስ ​ቢሆንም ግን በዚያው መስሪያ ቤት ውስጥ እንደ ልዑል ሰገድ ያልሆኑ፣ የህዝብ አደራን እንደ ክብር የሚያዩ ብዙ "ንጹሃን" አሉ። ከልዑል ሰገድ ሁለት ቢሮ ወረድ ብሎ የሚቀመጠው አቶ በቀለ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው። አቶ በቀለ በመስሪያ ቤቱ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ አገልግሏል። ልክ እንደ ልዑል ሰገድ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ በደቂቃዎች ውስጥ "በእጅ መንሻ" መውሰድ የሚችልበት እድል ቢኖረውም፣ እሱ ግን ምርጫው የህሊና ሰላም ነው።

​አቶ በቀለ ዛሬም ድረስ የሚኖረው በኪራይ ቤት ውስጥ ነው፤ ወደ ስራውም የሚመላለሰው በታክሲ ተጋፍቶ ነው። ልዑል ሰገድ በአንድ ዓመት ህንጻውን ሲያጠናቅቅ፣ አቶ በቀለ ግን አሁንም ለልጆቹ የደንብ ልብስና የቤት ኪራይ ለመክፈል ወር መጨረሻን በጉጉት ይጠብቃል።
​የሁለቱ መንገዶች ልዩነት ​የነጋዴው ልጅ በአባቱ ንግግር ላይ ትልቅ ቁምነገር አክሎ እንዲህ አለ
​"አባቴ ሆይ! ሁሉም የገቢዎች ሰራተኛ ግን እንደ ልዑል ሰገድ አይደለም። እንደ አቶ በቀለ ያሉ በድህነት ውስጥ ሆነውም ቢሆን ሀገራቸውን የማይከዱ፣ 'ከሰው ስጋ ይልቅ የላብ ገንዘብ ይጣፍጣል' ብለው የሚያምኑ ቅኖች አሉ። የልዑል ሰገድ ህንጻ በፍጥነት ቢያድግም፣ ውስጡ ግን በስጋትና በጭንቀት የተሞላ ነው። የአቶ በቀለ ህይወት ግን ምንም እንኳን ጎጆ ቢሆንም፣ ሀበውስጡ ሰላምና በረከት አለ።"

​አበው ለዚህ የሚሆን ግሩም ምሳሌ አላቸው፦
​"ካልተረገመ አፈር፣ አይበቅልም ወርቅ" ይባላል። ​ልዑል ሰገድ ከሰዎች እምባና ስቃይ የገነባው ህንጻ መጨረሻው ምን እንደሚሆን አይታወቅም። አንዳንዱ በወረርሽኝ፣ አንዳንዱ በህግ፣ አንዳንዱ ደግሞ በቁጭት ይፈርሳል። የአቶ በቀለና የነጋዴው ድካም ግን መሠረቱ ጽኑ ነው።

​በመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ የሚሰሩ ሁሉ ሌቦች አይደሉም። በልዑል ሰገድ ዙሪያ ያሉ ብዙ ታማኝ ሰራተኞች የልዑልን የቅንጦት ኑሮ እያዩ "እንዴት?" ቢሉም፣ የገዛ ህሊናቸውን ግን ለገንዘብ አይሸጡም። ታሪኩ የሚያስተምረን ዋናው ቁምነገር፦ ሀብት በፍጥነት ማደጉ ሳይሆን፣ እንዴት መጣ? ለዚህ ደግሞ የጀመርነው የፀናት ትግላችን ይቀጥላል
አቶ በቀለ ያልነው የባለሙያወን ስም ላለመጥራት ነው🤔በፌስቡክ የመጣነው የውስጥ ትግላችን ጭቆና አፈና ማስፈራት ስለ ገጠመው ነው በሀላፊው እና ከግማሽ በላይ የማኔጅመንት አባላት ስለዚህ በማይመጥነው ስብእናችን በፌስቡክ የምንልክልህ እንቀጥላለን አስተላልፍልን🙏

ደሴ ከተማ ዝረፍ ትወደሳለህ ነው ነገሩ!!!የደሴ ከተማ ገቢዎች የክትትል ቡድን መሪ ልኡል ሰገድ የሚባለዉ ከተመደበበት አላማ ዉጪ ነጋዴዎችን ከሀላፊው መላኩ ሚካኤል ጋር በመመሳጠር ጭምር  በ...
18/01/2026

ደሴ ከተማ ዝረፍ ትወደሳለህ ነው ነገሩ!!!
የደሴ ከተማ ገቢዎች የክትትል ቡድን መሪ ልኡል ሰገድ የሚባለዉ ከተመደበበት አላማ ዉጪ ነጋዴዎችን ከሀላፊው መላኩ ሚካኤል ጋር በመመሳጠር ጭምር በግብይት መረጃ ሲመጢ ከ1 ሚዮን ላይ 250 አምሳ ሽብር ለሱ ከሰጠህ የግብይት መረጃው ይጠፋልሀል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በክትትል ሰአት ብር ካልሰጣችሁኝ ደረሰኞቻችሁን 50 ሺብር ቅጣት እሰጠሀለሁ ደግሜ ቀጥቼ ሰነድህ ውድቅ አደርገዋለሁ በማለት ደረሰኝ የሚያግተዉ ሌባ እንደራደር እየለ በማስፈራራት ከብዙዎች ዳጎስ ያለ ብር ሲቀበል ቆይቷል ይሄን የሚያውቀው መላኩ ሚካኤል ድሮ መስርቶት ከነበረው ከውጫሌ እስከ ውርጌሳ የልጅነት የሌብነት ጥምረት ደሴ ከተማ ላይ በድጋሜ ለመምስረት ሲጣጣር ይታያል ከነገረ ቀደም መላኩ ሚካኤል ወረዳ ላይ በሌብነት ተፈርጆ በዛን ዘመን ግምገማ 4 አግኝቶ ህዝቡ መሮት በደቦ ይወጣል ተብሎ ወደ አገሩ ደቡብ ጎንደር ሊሄድ ሲሞክር አፍጫህን ላስ ብለው ይተፉታል መከረኛዋ ደሴ ተቀብላ ከቫዚል ፀጉር ፍረዛ ወደ ጄል አሸጋገረችው ይሄም ሳይበቃ ጩሆ በመናገር ብቻ እስከ ከንቲባ ማእረግ አበቃችው ከምእራብ ጎንደር ድረስ በማምጣት ሙሉ ቤተሰቡን የመንግስት ፈንድ በጥቃቅን እያደራጀ ብድር ወስደው እንዲጠፉ አደረገ ከአማች እስከ ውሽማወቹ ሼድ አልቀረ ኮንቴነር ሲያድል ከርሞ ዛሬ ደግሞ ከነ ልኡል እና ሀይሌ ስላሴ አይሲቲው ጋር ገጥሞ ሂሳብ ላይ ደግሞ በፍፁም ሌብነት ከሰሜን ወሎ እስከ ክልል ገቢዎች ድረስ የሚታወቀው እሸቱ ሌባው ጋር ተጣምሮ ተቋሙን በግሉ ፍላጎቱ አደራጅቶ ሲዘርፍ ከውስጥም ከውጭም ትግል ሲገጥመው ከንቲባው የራሱን ሌብነት ረስቶ እኔ ላይ አፈጠጠ እያለ በሰራተኛ ፊት ለሌቦቹ ለነ ልኡል ሀይሌ እሸቱ ቆሞ ይከራከራል ምክትል ከንቲባው አቶ ሽመልስ ሌቦቹን ለይቶ ቀንድ ቀንዳቼው ሲላቸው መላኩ ተከፋ እነሱ ሲኖሩ ምላሱ ይታጠፋል እነሱ በሌሉበት ደግሞ ማንም አይነካችሁም እያለ በሰራተኛ ፊት የብዙ ጨዋ ሰራተኞኝን ሞራል ይነካል
አቶ መላኩ ልኡልሰገድ የገነባው የአድማ ብተናው ቤት እንዴተ ተሰራ አንተ እንደምትለው ውጫሌ ሀይቅ ቤት ሽጧ ደሴ ገዛ ነው የምትለን አንድ እውነት የምንነግርህ ሀይቅ ላይ በዚህ ሰአት አሁን ወቅታዊ ገበያ 400 ካሬ ከነ ሙሉ ሰርቢሱ 1.8 ሚሊዮን ነው ልኡል የገነባው ቤት ግን ዋጋ ስንት ነው? ይገባናል የአንተ ቤት ተገንብቶ ባለ መጠናቀቁ ምክንያት እና ልኡል ጋር መካካድ መጀመራችሁ አስከፍቶሀል እሱ አይመለከተንም እኛ በድህነት የምንኖር ሰራተኞች በእናተ ሌብነት ፀብ ምክንያት መታወክ የለብንም ነው

በዚህ መሰረት ከደሴ ነጋዴ አላግባብ ከህግ አሰራር ዉጪ በሙስና በሰበሰበዉ ዳጎስ ያለ ብር ህንፃ ገንብቶ እንካችሁ ብሎናል ። ልዑል ሰገድን አድማ ብተና ያስገነባዉ ከነ ህንፃዉ ለጥፌላችኋለሁ መቸም የደሴ ነጋዴ ሁኖ የማያውቀዉ አለ ብየ አላስብም ምክንያቱም ያላስመረረዉ የለም።

ከዚህም ጋር ተያይዞ አንድ ቀን የሌብነቴ ጉድ መዉጣቱ አይቀርም በማለት ከባንክ ሚሊየኖች ተበድሮበታል።

እናም የደሴ ከተማ አስተዳደር ሰሞኑን ልኡል ሰገድ ይሄን ቤት ለመሸጥ ከመላኩ ጋር ፈቃድ ወስዶ ከተቋሙ ከጠፋ ወር ያልፈዋል እና ከደሴ ከተማ ህዝብ ተዘርፎ የተገኘው ሀብት ለከተማዋ ገቢ መሆን ስላለበት መታገድ አለበት የሀይቁ ቤት ስንት እንደተሸጠ ደሴ ያለውን ስንት እንደተገዛ ሌላው ገንዘብ ከየት እንደመጣ በቀጣይ በግልፅ እናስቀምጣለን
አቶ መላኩም ለሚሰትህ ነጋዴዎች አዋተው የሰጡህን ገንዘብ እስከ ወፍጮ ቤቱ እና ባህር ዳር ደሴም የመኖሪያ ቤቱ "ወፍጮ ቤቱን ጨምሮ ግንባታህ በዝርዝር እንመለሳለን ለአሁኑ ልኡል ሀይሌን እሸቱን አታድናቸውም እስከ መጨረሻው እንታገላለን!

ይሄን የመሰለ ቤት ጠቅላይ ሚኒስተሩ አብይ አህመድም አይኖራቸውም ለዝንየ የሰሩላት በፍፁም 👇👇👇

ከፋኖ ቀጥሎ የምናጠራው አለመረጋጋት ለሌብነት የሚጠቀሙን ነው!
ምንጭ Wollo Times ወሎ ታይምስ

Omar Ibn Mohammed
Mekdelawit Bayeh
ወርጤ ጦረኛው
Seifu Abdul Aziz



#እምየደሴ




#እምየደሴ


#ሃያትያረሱለላህ
#አይጠየፍወሎደሴ

#ሊጋባውበየነ
#ጥንቅሹቦርከናዊእሸት
#አማራነፃአውጭ

#አሊወሎ

ይህ አሳሳቢ ጉዳይ ነው ሰሚ ካለ። አንድ ተቋም መሪ ሲሆን ዋነኛው ተግባሩ ሰራተኛውን ማስተባበር፣ ግልጽ አሰራር መዘርጋት እና ለከተማዋ እድገት የሚበጅ ስራ መስራት መሆን ሲገባው፤ በስራ ባል...
17/01/2026

ይህ አሳሳቢ ጉዳይ ነው ሰሚ ካለ። አንድ ተቋም መሪ ሲሆን ዋነኛው ተግባሩ ሰራተኛውን ማስተባበር፣ ግልጽ አሰራር መዘርጋት እና ለከተማዋ እድገት የሚበጅ ስራ መስራት መሆን ሲገባው፤ በስራ ባልደረቦች እና በአመራሮች መካከል ክፍተት መፍጠር ለስራው እንቅፋት እንደሚሆን የታወቀ ነው።

​📢 ለደሴ ከተማ ነዋሪዎችና ለሚመለከተው አካል የቀረበ ግልጽ መልዕክት!
​ የተቋም መሪ ወይንስ የክህደትና የሀሜት ተራ ወሬ ስንመራ እንኑር ሰለቼን
​በደሴ ከተማ የገቢዎች መምሪያ ውስጥ እየታየ ያለው አሳፋሪ ድርጊት ከቀን ወደ ቀን እየባሰበት መጥቷል። የአንድ ተቋም ሀላፊ ዋነኛ ስራው ተቋሙን በብቃት መምራት፣ ግብር በአግባቡ እንዲሰበሰብ ማድረግና ለከተማዋ እድገት መስራት ሲሆን፤ የገቢዎች ሀላፊው አቶ መላኩ ሚካኤል ግን ስራቸውን ትተው "አለቆቼን ካልተቸሁ" በሚል ተግባር ተጠምደዋል።

የአመራር ክፍተትና ሀሜት ባለቤትነት አቶ መላኩ ሚካኤል ሰራተኞችን ሰብስበው ስለ ስራ ስኬት ከማውራት ይልቅ፣ የከተማዋን ከንቲባና ምክትል ከንቲባን በሰራተኞች ፊት ማማትና ስማቸውን ማጠልሸት ዋነኛ ተግባራቸው አድርገውታል።

የሌብነት ጥበቃ ጠበቃው መላኩ ሚካኤል በሙስናና በሌብነት የተጠረጠሩ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ "ከዚህ በኋላ ማንም ጣልቃ እየገባ አያስርም፣ እኔ አቅም አለኝ" በማለት ለሌቦች ከለላ ለመሆን መሞከራቸው ህዝብንና መንግስትን የናቀ ተግባር ነው።

የሰራተኛ ስነ-ልቦና መግደል ማስፈራራት አቅለሸለሸን "የ6 ወር እቅድ እገመግማለሁ" በሚል ስም ሰራተኛውን ማሸማቀቅ፣ መሳደብና በዛቻ ስራን ለማስኬድ መሞከር የተቋሙን ምርታማነት እያወረደው ይገኛል።

ለከተማዋ እድገት እንቅፋት የመሆን ቀጥተኛ ቃል መጠቀም ጀምሮል የደሴ ህዝብ ልማት በሚፈልግበት በዚህ ወቅት ግብርን በፍትሀዊነት ከመሰብሰብ ይልቅ በውስጥ ሴራና በአመራሮች እና ባለሙያወች መካከል ቅራኔ በመፍጠር ጊዜ ማጥፋት ለከተማዋ ትልቅ ኪሳራ ነው።

አንድ የመንግስት ሀላፊ ለዛውም ምክትል ከንቲባና እና ከንቲባው በሌሉበት አለቆቹን የሚያማው፣ በሙስና የተጠረጠሩትን የሚከላከለውና ሰራተኛን የሚያሸማቅቀው እስከመቼ ነው? የከተማው አስተዳደር ይህንን ግለሰብ በቅርብ ሊከታተለውና አስፈላጊውን እርምጃ ሊወስድ ይገባል!
​"ተቋም መምራት ያቃተው ሁሉ አለቆቹን ሲያማ ይውላል!"እኛ ደግሞ ሰለቼን አማራጭ ስናጣ በሶሻል ሚዲያ ነው ሰሚ ያለው ሲባል ሳንፈልግ መተናል እናዝናለን በጣም! ከዚህ በሆላም አንመለስም እንቀጥላለን ተጎጅዎች ነን እና ህግ እና ስረአት ሲከበር እናቆማለን ሌቦችንም በስም በፎቶ ጭምር እናሳያለን።
የደሴ ከተማ የገቢ እድገት የሚመጣው በስራ እንጂ በሀሜትና በዛቻ አይደለም አቶ መላኩ ሚካኤል።
​ #ደሴ #ፍትህ

Address

Tata
Tanta

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አሚር አል-ሙእሚኒን Amir Al-Mu'minin posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share